07.11.2014 Views

Awra Amba RJ 300612 EN - Contacter un comité local d'Attac

Awra Amba RJ 300612 EN - Contacter un comité local d'Attac

Awra Amba RJ 300612 EN - Contacter un comité local d'Attac

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

<strong>Awra</strong> <strong>Amba</strong>, a current experiment of utopian socialism <br />

መግለጫ <br />

አውራ አምባ፡ ወቅታዊው ኅብረተ ሰብአዊ አንዋንዋር፡፡ <br />

በበኅብረትና በእኩልነት ለመኖር ሲደረጉ ከቆዩት ሙከራዎች ሁሉ፡ ኢትዮጽያ የሚገኘው አውራ አምባ ተብሎ የሚሰየመውና በአማራው <br />

ክፍለ ሀገር ውስጥ የሚገኘው ህብረተ ሰብ በእኩልነትና በኅብረተሰብአዊነት ላይ የተመሰረተ ነው ። <br />

ይህ ጽሁፍ፡ ስለ ኅብር ሰቡ የተጻፉትን ልዩ ልዩ ጥናቶችን ፡ ማለትም አራት የማስተሬት የምርምርም ዘገባዎችን (አጥናፉ 2005 ፥ ይርጋ <br />

2007 ፥ ያሲን 2008 ፥ መኮንን 2009) ያቀነባበረ ሲሆን ፥ በተጨማሪም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የጋዜጣ ዘገባዎችንና <br />

ምስክሮችን ያካትታል ። በመጀመሪያ የራሳችንን አቀራረብና አመለካከት ፡ ማለትም የተመሮከዝንባቸውን የተለያዩ ምንጮችን የግል <br />

አስተያየትና ትችታችንን እያከልን እናቀርባለን ፥ አዚያም ከተለያየ አቅጣጫ የሰበሰብናቸውና የንደዚህ አይነቱን የአንዋንዋር ዘዴ <br />

በትክክል እንድናቀርብ ያገዙንን መረጃዎች እነዘረዝራለን ። ይህም ሲሆን አመቺ በሆነ ጊዜ ሁሉ አካባቢው ካለው የአማራ ኅብረተሰብ ጋር <br />

ለማስተያየት እንሞክራለን ። <br />

ኅብር ሰቡ የተጠነሰሰው በዙማ ኑሩ በ1972 ዓ/ም ነው። ገና በጨግላነቱ፡ ይህ ደሀ የባላገር ልጅ አርቆ አሰተዋይ በመሆኑ ፥ አካባቢውም <br />

ሆነ እቤተሰቡ ውስጥ የተመለከታቸው ጎጂና ከሀቅ የራቁ ድርጊቶችን በመቃወም ለእኩልነት ይታገል ጀመረ ። በክፍለ ሀገሩም እየዞረ <br />

ሀሳቡን የሚደግፉ ሰዎችን መፈለግ ጀመረ ። በመጨረሻም፡ ወደ ሃያ የሚጠጉ ሰዎችን ሰብስቦ ፥ የአውራ አምባ ህብረ ሰብን በህምሳ <br />

ኤክታር ላይ ያቅዋቁማሉ ። ይሁን ብንጂ፥ ከአካባቢው ነዋሪዎች ከፍ ያለ ቅዋሜ ይደርስባቸዋል ። ምክንያቱም የአውራ አምባ ህብረ ሰብ <br />

ከሀይማኖት ነፃ ከመሆኑም በላይ ፥ የሴትና ወንድ እኩልነትንም ሆነ የልጆችን መብት የሚያስከብር በመሆኑ ። ከዚያም በኢተዮጰያ ውስጥ <br />

የተከሰተው ለውጥ ህብረ ሰቡን ከመበታተኑም በላይ ፥ ዋና መሪውን እስር ቤት በማስገባትና ለብዙ ዓመታት ርቀው በስደተኝነት እንዲኖሩ <br />

ያስገድዳቸዋል ። በ1993 ዓ/ም ህብረ ሰቡ ተመልሶ አሁን የሚገኝበት ቦታ ላይ ከንደገና ይደራጃል ። <br />

በተለያዩ ደራሲያን የመዘገቡትን ቁጥር ስንመለከት የአውራ አምባ ህብረ ሰብ ሲጀመርና በስደት ጊዜ ከሃያ በታች የነበረው በአሁኑ ወቅት <br />

ከአራት መቶ በላይ መሆኑን ያስገነዝባል ። አቀነባበራቸውን በፆታና በእድሜ አካባቢው ከሚገኘው ከደቡብ ጎንደር ህዝብ ጋር <br />

እናስተያያለን ። ከዚያም በኢትዮጵያ ውስጥ የአውራ አምባ ኅብረ ሰብ ምን አይነት ቦታ እንደያዘ እናሳይና ፥ በቦት አቀማመጥ በህዝብ <br />

ቁጥርና በኢኮኖሚ ረገድ ያለውን ልዩነት እናመለክታለን ። <br />

የአውራ አምባ በባህልና በአስተሳሰብ አንድነት የሰፈነበት መንደር ሲሆን ፥ አካባቢው ከሚገኘው የአማራ ብኄረ ሰብ በጣም የተለየ ነው ። <br />

በመጀመሪያ ኅብረ ሰቡ ብዙ ዕሴቶች አሉት ፥ በአውራ አምባ መኖር ማለት ዕሴቶቹን ማክበርና ማስከበር ነው ። የተለያዩ ደራሲያን <br />

የጠቀሱአቸው ዕሴቶች በርካታ ቢሆኑም ፡ ዋንኞቹን በተደጋጋሚ የሚጠቀሱት ሀቀኛነት፡ እኩልነት በተለይም የሴትና ወንድ እኩልነት፡ <br />

ኅብረተሰብአዊነት፡ ሥራና የሀይማኖት አለመኖር ናቸው ። ይህንኑ የአውራ አምባ ኅብረተሰብ እንዴት እንደሚያከብርና እንደሚያስከብር <br />

በቅድመ ተከተል ደራሲያን የመዘገቡት ጽሁፍ ላይ በመመርኮዝ እናብራራለን ። <br />

በመቀጠልም የኅብረ ሰቡን የረቀቀ አቀነባበር እናሳያለን ። በቅድሚያ የኅብረ ሰቡን ግንባታና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንመዘግብና ከዚያ <br />

የኅብረ ሰቡን የአንዋንዋር ስልት በሚመለከት የሚከተሉትን እንዘረዝራለን ፡፡ ይኸውም በሥራ መስክ ላይ ያለውን የሴቶችና ወንዶችን <br />

እኩልነት ፥ ጋብቻና ፍችን በሚመለከት ፥ ለልጆች የሚሰጠው የተወሰነና ልዩ ቦታ ፥ ከአቅም ደካሞች ጋር ያለው ትብብር ፥ የቀብር <br />

ሥርአትና በመጨረሻም በኅብረ ሰቡ ውስጥ የሚከሰተውን ችግር አፈታት ይሆናል። <br />

የአውራ አምባን አደረጃጀት በሚመለከት፥ ኅብረ ሰቡ በሁለት ይዋቀራል ። አንደኛው አጠቃላዩ ተከባብሮና ተደጋግፎ የሚኖረው ኅብረ <br />

ሰብ ሲሆን ፥ ሁለተኛው በሥራ መስክ ተሳትፎ የሚያደርገው የኅብረ ሰቡ ሦስት አራተኝ ነዋሪ ይሆናል ። የኅብረ ሥራ ማህበሩ ዋና ዋና <br />

ውሳኔዎች በአጠቃላይ ጉባዔው ይወሰናሉ ። ይህ ጉባዔ የሚመርጣቸው ኮሚቴዎች በየመስካቸው የተለያየውን ሥራ ጉባዔው በወሰነው <br />

መሰረት በህብረት ያካሂዳሉም ይቆጣጠራሉም ። 44 % የኮሚቴው አባላት ሴቶች ናቸው ፡ አሰፈላጊ በሆነ ጊዜም ይቫራሉ ። <br />

የአውራ አምባ ማህበር ኤኮኖሚ በከፊል ግብርና ነው ። ይሁን እንጂ ያላቸው የእርሻ መሬት ከአካባቢው መሬት ጋር ሲነጻጸር በጣም <br />

አነስተኛ ነው ፡ ከተለያዩ ጽሁፎች እንደምንረዳው ፡ የአውራ አምባ ነዋሪዎች በቤተሰብ ከ0,2 እስክ 0,4 ሄክታር ሲኖራቸው ፥ የአካባቢው <br />

በቤተሰብ 2,1 ሄክታር ይኖረዋል ። ዋናው የእርሻ ምርት ጤፍ ቦቆሎ ማሽላና ቦሎቄ ሲሆን በተጨማሪም አነስተኛ የከብት እርባታም <br />

ይገኝበታል ። ውጤታቸው ከአካባቢው በአንድ አራተኛ ከፍ ይላል ። ይሁን እንጂ ምርታቸው ለፍጆታቸው ሰለማይበቃ ወደ ተለያዩ እንድ <br />

ሸማኔ የወፍጮና ንግድ መስክ ተሰማርተዋል ። ባብዛኛው ሥራው የሚካሆደው በኅብር ሥራ ማህበሩ ውስጥ ነው ፥ ነገር ግን ዋናውን <br />

የሽመና ሥራ እያንዳንዱ በቤቱ ስለሚሠራ የግል ሥራ ሆኖ ይገኛል ። <br />

እኒህ የተለያዩ የገቢ ምንጮች ለኅብረ ሰቡ ካካባቢው የተሻለ ገቢ የሚያስገኝ ቢመስልም ፥ የተመዘገበው ቁጥር አስተማማኝ ካለመሆኑም <br />

በላይ አንዳንድ ቦታ ላይ ተቃራኒ ሆኖ ይታያል ። ሆኖም የነዋሪው የእለት ምግብ አመቱን ሙሉ የተማላ ይመስላል ። አካባቢው ያለው <br />

አማራው አርሶ አደር ግን የሚሸፍነው ባመት የዘጠኝ ወር ቀለቡን ብቻ ነው ። <br />

ከዚህ በመቀጠል እያንዳንዱ የኅብረ ሰብ አባል በተለያየው የሥራ መድረክ ላይ የሚያደርገውን አስተዋጽዎ እናብራራለን ። ባብዛኛው <br />

8 /85

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!